ደቡብ ኦሤትያ-አላኒያ (ኢሮንኛ፦ /ኹሣር ኢርስቶን-አሎንስቶን/) በከፊል ተቀባይነት ያገኘ አገር ነው። ነጻነቱን በ1983 ዓ.ም.
ያዋጀ ምንም ቢሆን፣ ጂዮርጂያ ግን ይግባኝ አለው።
ከተባበሩት መንግሥታት የሚከተሉት አገራት ደቡብ ኦሤትያን ተቀባይነት ሰጥተዋል፦ ሩስያ፣ ኒካራጓ (በ2000 ዓ.ም.) ፤ ቬኔዝዌላ (2001 ዓ.ም.)፣ ናውሩ (2002 ዓ.ም.)፣ ሶርያ (2010 ዓ.ም.)
በከፊል ተቀባይነት ካገኙት ሌሎች አገሮች፣ አብካዝያ፣ ትራንስኒስትሪያ እና አርጻኽ (የቀድሞው ናጎርኖ-ካራባቅ) ደቡብ ኦሤትያን እርስ በርስ ይቀበላሉ። ምዕራባዊ ሣህራ ደግሞ ደቡብ ኦሠትያን ተቀብሏል።
በተጨማሪ ቱቫሉ ከ2003 እስከ 2006 ዓ.ም. ድረስ ይቀበለው ነበር።
የተረፉት መንግሥታት የጂዮርጂያ ግዛት እንዲሆን የጂዮርጂያን ይግባኝ ተቀባዮች ናቸው።
በመጋቢት 2009 ዓም ከተደረገው ሕዝቡ ውሳኔ ቀጥሎ የሀገሩ ስም በይፋ ከ «ደቡብ-ኦሤትያ» ወደ «ደቡብ-ኦሤትያ-አላኒያ» ተቀየረ። የአገሩ ሕዝብ ከታሪካዊ አላኖች ብሔር እንደ ተወለደ ይታመናል፤ ታሪካዊውም አላኒያ ከ890-1230 ዓም ያሕል በአካባቢው የቆየ መንግሥት ነበረ።
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article ደቡብ ኦሤትያ-አላኒያ, which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.