ዶ/ር ተወልደብርሃን ገብረእግዚኣብሔር የእጽዋት ጄኔቲክ ሃብት ለንግድ ሲባል እንዳይለወጥና በተለይ ሰለጠኑ የሚባሉት ኣገሮች የገበሬው ሕብረተሰብ ለዘመናት ጠብቆ ያቆየውን እንዲያከብሩ ተከራክረዋል። ይህ መብት እንዲከበርና የእጽዋትን ጂን እየቀየሩ በፓተንት በመጠበቅ ችግር እንዳይፈጥሩ ኣስተባብረዋል።
ለዶ/ር ተወልደ “ራይት ላይቭሊሁድ አዋርድ” የተባለው ሽልማት በ፲፱፻፺፫ ዓ.ም. ተሰጥቷቸዋል። በእዚህ መስክ ይህ ሽልማት ለዶ/ር መላኩ ወረደ ከመሰጠቱ ሌላ በእንዶድ ምርምር ዶ/ር አክሊሉ ለማ እና ዶ/ር ለገሠ ወልደዮሓንስ ተሸልመዋል። ይህ የዕውቅና ሽልማት የኖቤል ሽልማት በማይሰጥበት መስክ ስለሆነ ኣማራጭ ነው ይባላል።
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article ተወለደ ብርሃን ገብረ እግዚአብሔር, which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.