የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፬: ዘቅዱስ ሕርያቆስ | |
---|---|
ዘቅዱስ ሕርያቆስ |
፲፰ ፤ ይልቁንም በዚች ቦታ ስለሞቱ አንቺ ስለነርሱ ተግተሽ አማልጂ ነፍሳቸውን ዕረፍት ሰጥቶ ያሳርፍ ዘንድ ።
፲፱ ፤ የድል ነሺዎች የሰማዕታት ቦታ በተባለ ሁሉ ዘንድ በብሩካን ጻድቃን ቦታና በትጉሀን መላእክት ቦታ በቦታው ሁሉ ዘንድ አንቺ ርስት ነሽ ስምሽም በእግዚአብሔር ዘንድ የሠለጠነ ነው ።
፳ ፤ የተቀመጣችሁ ተነሡ
፳፩ ፤ እግዚአብሔርን በመፍራት እንነሣ ምስጋናን የተመላች እርስዋን ከፍ ከፍ እናደርጋት ዘንድ እንዲህም እያልን እናመሰግናት ዘንድ ጸጋን የተሞላሽ ሆይ የደስታ መፍሰሻ ሆይ ዓይኖቻቸው ብዙዎች ከሆኑ ከኪሩቤል ክንፎቻቹው ስድስት ከሚሆኑ ከሱራፌል ይልቅ የሚበልጥ የመልክ ግርማ አለሽ ።
፳፪ ፤ ወደ ምሥራቅ ተመልከቱ ።
፳፫ ፤ እግዚአብሔር አብ በሰማይ ሆኖ ምሥራቅንና ምዕራብን ሰሜንና ደቡብን ዳርቻዎችንም ሁሉ በእውነት ተመለከተ ተነፈሰ አሻተተም እንድ አንቺ ያለ አላገኘም ። የአንቺን መዓዛ ወደደ ደም ግባትሽንም ወደደ ። የሚወደውን ልጁን ወደ አንቺ ሰደደ ።
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፬, which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.