አብካዝያ (አብካዝኛ፦ /ኣጵስንይ/) በከፊል ተቀባይነት ያገኘ አገር ነው። ነጻነቱን በ1984 ዓ.ም.
ያዋጀ ምንም ቢሆን፣ ጂዮርጂያ ግን ይግባኝ አለው።
ከተባበሩት መንግሥታት የሚከተሉት አገራት አብካዝያን ተቀባይነት ሰጥተዋል፦ ሩስያ፣ ኒካራጓ (በ2000 ዓ.ም.) ፤ ቬኔዝዌላ (2001 ዓ.ም.)፣ ናውሩ (2002 ዓ.ም.)፣ ሶርያ (2010 ዓ.ም.)።
በከፊል ተቀባይነት ካገኙት ሌሎች አገሮች፣ ደቡብ ኦሤትያ-አላኒያ፣ ትራንስኒስትሪያ እና አርጻኽ አብካዝያን እርስ በርስ ይቀበላሉ።
በተጨማሪ ቫኑአቱ ከ2003 እስከ 2005 ዓ.ም. ድረስ አብካዝያን ይቀበል ነበር። እንዲሁም ቱቫሉ ከ2003 እስከ 2006 ዓ.ም. ድረስ ይቀበለው ነበር።
የተረፉት መንግሥታት የጂዮርጂያ ግዛት እንዲሆን የጂዮርጂያን ይግባኝ ተቀባዮች ናቸው።
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article አብካዝያ, which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.