ኮካ-ኮላ (ወይም ኮካ) በአለም ዙሪያ የሚሸጥ ለሥላሣ መጠጥ ነው።
ኮካ-ኮላ መጀመርያ የተፈጠረ በ1878 ዓ.ም. በአትላንታ አሜሪካ በዶ/ር ጆን ፔምበርቶን ነበረ። መጀመርያ ሀሣቡ ማነቃቂያ መድኃኒት እንዲሆን ነበር። ኮካ-ኮላ የሚለው ስም የተወሰደበት ምክንያት በመጀመርያ የኮካ ቅጠልና የኮላ ፍሬ በውስጡ ስለነበረ ሲሆን፣ ዛሬ ግን እነዚህ አትክልት አይገኙበትም።
ከ1886 ዓ.ም. ጀምሮ በብርሌ ይሸጥ ጀመር። በ1947 ዓ.ም. ደግሞ በቆርቆሮ ይሸጥ ጀመር።
ዛሬ የኮካ-ኮላ ድርጅት ብዙ ሌሎች አይነት ለሥላሣዎች ይሠራል። በአለም ዙሪያ በ1 ሴኮንድ ውስጥ፣ ከኮካ-ኮላ ድርጅት የወጡ የ10,450 ለሥላሣዎች እየተጠጡ ነው።
ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article ኮካ ኮላ, which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.