ንጉሥ ሣህለ ሥላሴ የሸዋው መስፍን የራስ ወሰን ሰገድ እና የመንዝ ባላባት የአፍቀራ ጎሌ ልጅ የወይዘሮ ዘነበ ወርቅ ልጅ ናቸው። በዘመኑ ኢትዮጵያን አንድ አድርጎ የሚገዛ ምኒልክ የሚባል ንጉሥ ይነግሣል የሚባል ንግርት ስለነበር፣ አባታቸው ምኒልክ ብለዋቸው ነበር። ሣኅለ ሥላሴ ትምህርታቸውን በሰላ ድንጋይ ደብር ሲከታተሉ ከቆዩ በኋላ አባታቸው ራስ ወሰን ሰገድ ቁንዲ ላይ ሰኔ ፩ ቀን ፲፰፻፭ ዓ/ም ላይ ሲያርፉ የሸዋን አልጋ አውርሰዋቸው አለፉ። ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ ‘የኢትዮጵያ ታሪክ ፦ ከንግሥተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል በሚለው መጽሐፋቸው በገጽ ፷፭ ላይ “የራስ ወሰን ሰገድ የበኩር ልጅ አቤቶ በኩሩ የመርሐቤቴን አበጋዝነት ተሾሞ ይኖር ነበርና በአባቱ አልጋ እንዲቀመጥ ተጠርቶ ጅሩ ሲደርስ የጅሩ ጋላ /ኦሮሞ/ መንገዱን ዘግቶ ስምንት ቀን ሙሉ ስለተዋጋው ሳይመጣ ቢቆይ የወሰንሰገድ መኳንንት ባልጋው ሰው ሳይቀመጥ ብዙ ቀን የቆየ እንደሆነ የጋላ//ኦሮሞ/ ኃይል በርትቶ ሸዋን በጭራሽ የሚያጠፋው ስለመሰላቸው፣ ታናሹን ልጁን አቤቶ ሣህለ ሥላሴን ከቁሮ ገደል /ከሰላድንጋይ/ አምጥተው በተወለደ በ፲፰ ዓመቱ በአባቱ አልጋ አስቀመጡት።” በሚል ትንሽ በተለየ መልክ አስቀምጠውታል።
ንጉሥ ሣህለ ሥላሴ | |
---|---|
ንጉሠ ሸዋ | |
ግዛት | ከጥቅምት ፪ ቀን ፲፰፻፵ እስከ ጥቅምት ፴ ቀን ፲፰፻፵፰ ዓ.ም. |
ቀዳሚ | ራስ ወሰን ሰገድ |
ተከታይ | ንጉሥ ኃይለ መለኮት |
ባለቤት | ወ/ሮ እጅጋየሁ ወ/ሮ ትደንቂያለሽ |
ሥርወ-መንግሥት | ሰሎሞን |
አባት | ራስ ወሰን ሰገድ |
እናት | ወ/ሮ ዘነበ ወርቅ ጎሌ |
የተወለዱት | 1824 እ.ኤ.አ. |
የሞቱት | ጥቅምት ፴ ቀን ፲፰፻፵፰ ዓ.ም. አታክልት |
ሀይማኖት | የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስትና |
ንጉሥ ሣህለ ሥላሴ ከብሪታኒያ መንግሥት ጋር አንጎለላ ላይ ኅዳር ፲ ቀን ፲፰፻፴፬ ዓ/ም የተፈራረሙት የወዳጅነትና የንግድ ውል በሰፊው የተዘገበ ሲሆን፤ ከፈረንሲስ ንጉሥ ጋር ደግሞ ተመሳሳይ ውል ሰኔ ፩ ቀን ፲፰፻፴፭ ዓ/ም ተፈራርመዋል።
ንጉሥ ሣህለ ሥላሴ የአራት ወንዶችና የአምስት ሴቶች ልጆች አባት ነበሩ። ከነኚህም፦
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article ሣህለ ሥላሴ, which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.