ፊታውራሪ ተክለ ሐዋርያት ተክለ ማርያም የኢትዮጵያ የሥነ ጽሑፍና የመንግሥት ሰው ነበሩ።
ለጊዜ የጅጅጋ እና የጨርጨር በአገረ ገዥነት ካገለገሉ በኋላ፣ በጅሮንድ (በኋላ ፊታውራሪ) ተክለ ሐዋርያት በ1923 ዓም ከኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት ደራሲዎች ዋናው ሆኑ። አጼ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በጻፉት ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ ውስጥ አንድ ወሳኝ ምዕራፍ ፴ «የሕገ መንግሥትን ትርጓሜ ስለ ማስረዳት።» በሙሉ ከበጅሮንድ ተክለ ሐዋርያት ቃላት ጠቀሱዋቸው። በዚህም ሰዓት ለጥቂት ወሮች በጅሮንድ ተክለ ሐዋርያት የገንዘብ ሚኒስትር ሆነው አገለገሉ። ለጊዜም የኢትዮጵያ መላክተኛ በብሪታኒያ ሆነዋል።
ከሕይወቴና ምዕራፍ ፴ ጠቃሚ የሆነ አጭር ጥቅስ ይከተላል፦
«ሰው እንዲጠቀምበት የሚፈቀድለት ነገር ሁሉ የጥቅም መብት ተብሏል። ይኸውም የጥቅም መብት በሁለት ዋና ክፍል ይለያያል።
«ለነዚህ ለተነገሩት በግልም በመተባበርም ለሚሆኑት ጥቅሞች ሁሉ ለደምሳሹ አሳብ ጃንሆይ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሕግ ሰጥተዋል። ዝርዝር ለሚሆነው አሳብ ግን አማካሪዎች በምክር ቤት በጉባኤ እያሰናዱ እንዲያቀርቡላቸው ከላይ እንዳሳየነው የመንግሥት አቋቋም መሠረት ሕገ መንግሥት የተባለውን ተክለዋል።»
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article ተክለ ሐዋርያት ተክለ ማርያም (ፊታውራሪ ), which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.