ፖርቶ ኖቮ (Porto-Novo፤ ደግሞ Hogbonou /ሆግቦኑ/፣ Adjacé /አጃሽ/ ተብሎ) የቤኒን ዋና ከተማ ነው።
የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር (1998 ዓ.ም.) 238,199 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 06°30′ ሰሜን ኬክሮስ እና 02°47′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።
ፖርቶ ኖቮ በድሮ 'አጃች' ሲባል የአጃ መንግሥት መቀመጫ ነበረ። የአሁኑ ስም ከፖርቱጊዝ ባርያ ፈንጋዮች በ17ኛ ክፍለ ዘመን ወጣ። እነሱ አንድ ጣቢያ እዚያ ሰርተው ነበር።
በኋለኛ ዘመን በ1855 ዓ.ም. እንግሊዞች አደጋ ስለ ጣሉ የፖርቶ ኖቮ መንግሥት የፈረንሳይ ጠባቂነትን ተቀበለ። ነገር ግን የጎረቤት ዳሆመይ መንግሥት የፈረንሳያውያንን ጥልቅ ማለት ስላልወደዱ ከሁለቱ መንግሥታት መካከል ጦርነት ሆነ። በ1875 ዓ.ም. የፈረንሳይ ባሕር ኃይል በፖርቶ ኖቮ ደረሰና ፖርቶ ኖቮ ወደ ፈረንሳይ ቅኝ አገር ወደ ዳሆመይ ተጨመረ። በ1892 ዓ.ም. የዳሆመይ መቀመጫ ሆነ።
ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article ፖርቶ ኖቮ, which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.