ለሰዎች በጎ ማድረግ ካልተቻለ ሰዎች እኛ ላይ ሊያደርጉብህ የማንፈልገውን ነገር በሌላው ላይ አለማድረግ ነው። ይህ ወርቃማ ሕግ ይባላል። ነቢያችን”ﷺ” ስለዚህ ወርቃማ ሕግ ሲናገሩ፦ “ከእናንተ አንድም አላመነም ለራሱ የሚወደውን ለወንድሙ እስካልወደደ ድረስ ወይም ለራሱ የሚወደውን ለጎረቤቱ እስካልወደደ ድረስ” ብለዋል፦ ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 77 አነሥ ኢብኑ ማሊክ”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ *”ከእናንተ አንድም አላመነም ለራሱ የሚወደውን ለወንድሙ እስካልወደደ ድረስ ወይም ለራሱ የሚወደውን ለጎረቤቱ እስካልወደደ ድረስ”*፡፡ يُحَدِّثُ عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ “ لاَ يُؤْمِنُ أَحَدُكُمْ حَتَّى يُحِبَّ لأَخِيهِ – أَوْ قَالَ لِجَارِهِ – مَا يُحِبُّ لِنَفْسِه ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 2, ሐዲስ 6 አነሥ”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ *”ከእናንተ አንድም አላመነም ለራሱ የሚወደውን ለወንድሙ እስካልወደደ ድረስ”*፡፡ عَنْ أَنَسٍ ـ رضى الله عنه ـ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم. وَعَنْ حُسَيْنٍ الْمُعَلِّمِ، قَالَ حَدَّثَنَا قَتَادَةُ، عَنْ أَنَسٍ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ “ لا يُؤْمِنُ أَحَدُكُمْ حَتَّى يُحِبَّ لأَخِيهِ مَا يُحِبُّ لِنَفْسِهِ
ኢማም ነወዊይ ይህንን ሐዲስ ሲያብራሩ፦ ሸርሑል አርበዒን 13
የራሱ ስሜት፣ ፍላጎት፣ አስተሳሰብ፣ አመለካከት እንዲነካበት የማይፈልግ የሌላው ሰው ስሜት፣ ፍላጎት፣ አስተሳሰብ፣ አመለካከት አይነካም። ይህ ወርቃማ የሥነ-ምግባር ሕግ የነቢያት ሁሉ አስተምህሮት ነው፦
ወርቃማው ሕግ በክርስትና አለም ማለት በተለይ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲህ ያስተማረው ቃል ነው፦
ጽንሰ ሀሣቡ ከብሉይ ኪዳን ከሕገ ሙሴ ዘመን ጀምሮ ይገኛል፣ ከዚያም በኋላ ተመሳሳይ መርኆች በሌሎች እምነቶች ወይም ፍልስፍኖች በጽሑፎቻቸው ታይተዋል። በጊዜ ላይ ተመሳሳይ ሀሳቦች በመላው ዓለም በመስፋፋት፣ እንዲህ ያለ መርኅ የብዙ ባህሎች ስነልቡናዊ እና ኅብረተሠባዊ መሠረት ሆንዋል። በተለይም፦
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article ወርቃማው ሕግ, which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.