፪ ቱትሞስ (ግብጽኛ፦ /ጀሁቲመስ/) ዓኸፐረንሬ በጥንታዊ ግብጽ የግብጽ አዲስ መንግሥትና የ18ኛው ሥርወ መንግሥት ፈርዖን ሲሆን ምናልባት 1501-1487 ዓክልበ.
የገዛ ነበረ።
ቱትሞስ ዓኸፐረንሬ | |
---|---|
የ፪ ቱትሞስ ስዕል በካርናክ ቤተመቅደስ | |
የግብጽ ፈርዖን | |
ግዛት | 1501-1487 ዓክልበ. |
ቀዳሚ | 1 ቱትሞስ |
ተከታይ | ሃትሸፕሱት |
ባለቤት | ሃትሸፕሱት፣ ኢሰት |
ሥርወ-መንግሥት | 18ኛው ሥርወ መንግሥት |
አባት | 1 ቱትሞስ |
2 ቱትሞስ የቀዳሚው የ1 ቱትሞስና የንግሥቱ ሙትኖፍረት ልጅ ነበር። የ2 ቱትሞስ ዋና ንግሥት ደግሞ ያባቱና የሌላይቱ ንግሥት አሕሞስ ልጅ ሃትሸፕሱት ነበረች። የ2 ቱትሞስ ቁባት ንግሥት ኢሰት ተባለች፣ እርሷም የተከታዩ 3 ቱትሞስ እናት ሆነች።
በማኔጦን መሠረት ለ13-14 ዓመት እንደ ገዛ ባብዛኛው ይቀበላል። አንዳንድ መምህሮች ግን ዘመኑ ከ3-4 አመት በላይ አይሆንም ይላሉ።
በ፪ ቱትሞስ ዓኸፐረንሬ ዘመን አባቱ ከኩሽ መንግሥት የያዛቸው የኖቢያ ግዛቶች ያምጹበት ነበር፤ እሱ ግን ሥራዊቱን ልኮ አስመለሠው።
የጦር አለቃው አሕሞስ ፐን-ነኽበት ደግሞ «ሻሱ» በተባለ ወገን ላይ ዘምቶ በርካታ ምርከኞች እንደ ያዘ ይላል። እነኚህ በደቡብ ከነዓን የተገኙት የኤዶምያስ ሰዎች ወይም ሌሎች እንደሚሉ ዕብራውያን ነበሩ። በተጨማሪ ሌላ የተገኘ ጽሑፍ እንዳለን ዓኸፐረንሬ በረጨኑ (ሶርያ) እስከ ኒይ ከተማ ድረስ ዘመተ። ወደ ሶርያ የደረሱ በመርከብ ወይም በመሬት እንደ ሆነ አልተገለጸም።
የ፪ ቱትሞስ ተከታይ በይፋ ልጁ ፫ ቱትሞስ ሲሆን እሱ ግን ገና ሕጻን ልጅ ሆኖ የቱትሞስ ንግሥት ሃትሸፕሱት ባለሙሉ ሥልጣን እንደራሴው፣ በቅርብም ጊዜ ውስጥ በራስዋ መብት ፈርዖን ተባለች። በ22ኛ ዓመትዋ (1466 ዓክልበ. ግ.) ዓርፋ ያንጊዜ ፫ ቱትሞስ ለብቻው ፈርዖን ሆነ።
ቀዳሚው 1 ቱትሞስ | የግብፅ ፈርዖን 1501-1487 ዓክልበ. | ተከታይ ሃትሸፕሱት |
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article 2 ቱትሞስ, which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.