የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፲፩: ዘቅዱስ ሕርያቆስ | |
---|---|
ዘቅዱስ ሕርያቆስ |
፷፰ ፤ ከፍጥረት ሁሉ እንደሚቀድም እንደ አዳም አንድ የምንል አይደለም በባሕርዪው አንድ ሲሆን ሦስት ነው እንላለን እንጂ ።
፷፱ ፤ ክፉዎች አይሁድ ባለማወቃቸው የእግዚአብሔርን ገፅና አካል አንድ ነው የሚሉ በደለኞችን የይስማኤል ወገኖችንም እነሆ እንሰማቸዋለን ልቦናቸውን ያሳወሩ ናቸው ።
፸ ፤ አምላኮቻቸውም ብዙ አጋንንቶቻቸው ብዙ የሆኑ በጣዖት የሚያመልኩ አረማውያንን እንሆ እናያቸዋለን ።
፸፩ ፤ እኛ ግን በጎ ጐዳና የሚያስተምሩትን እንከተላለን ። ሐዋርያት እንዲህ እያሉ እንዳስተማሩን ።
፸፪ ፤ አብ ፀሐይ ነው ወልድ ፀሐይ ነው መንፈስ ቅዱስም ፀሐይ ነው ። ከሁሉ በላይ የሚሆን አንድ የእውነት ፀሐይ ነው ።
፸፫ ፤ አብ እሳት ነው ወልድ እሳት ነው መንፈስ ቅዱስም እሳት ነው ። በልዕልና ያለ አንድ የሕይወት እሳት ነው ።
፸፬ ፤ አብ ጎሕ ነው ወልድ ጎሕ ነው መንፈስ ቅዱስም ጎሕ ነው ። በብርሃኑ ፀዳል ጨለማ የራቀበት አንድ የጧት ጎሕ ነው ።
፸፭ ፤ አብ ጒንደ ወይን ነው ወልድ ጒንደ ወይን ነው መንፈስ ቅዱስም ጒንደ ወይን ነው ። ዓለሙ ሁሉ የጣፈጠበት አንድ የሕይወት ወይን ነው ።
፸፮ ፤ አብ ሐሊብ ነው ወልድ ሐሊብ ነው መንፈስ ቅዱስም ሐሊብ ነው ። ጭማሪ የሌለበት አንድ ሐሊብ እርሱ ነው ።
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፲፩, which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.