ስሜን ቆጵሮስ (በይፋ፦ «የቱርክ ስሜን ቆጵሮስ ሪፐብሊክ»፤ ቱርክኛ፦ Kuzey Kıbrıs /ኩዘይ ክብርስ/) በቆጵሮስ ደሴት ላይ የምትገኝ አገር ናት።
በሐምሌ 8 ቀን 1966 ዓም የቆጵሮስ ግሪኮች ወገን የቆጵሮስ መንፈቅለ መንግሥት ስላካሄዱ፣ ስለዚህ በ13 ሐምሌ የቱርክ ሥራዊት በስሜን ወረረ፣ ጦርነቱም ከጨረሰ በኋላ የቱርኮች ወገን አስተዳደር በስሜኑ፣ የግሪኮችም በደቡቡ ቀርተው ነበር። በ1967 ዓም ስሜኑ «የቱርክ ቆጵሮስ ፌዴራላዊ ግዛት» ሆነ፣ በ1976 ዓም «የቱርክ ስሜን ቆጵሮስ ሪፐብሊክ» ሆነ።
ሆኖም ከቱርክ አገር በስተቀር፣ ከአንዳችም ሌላ አገር ምንም ዲፕሎማቲክ ተቀባይነት የለውም። በተረፈ ሌሎቹ አገራት በይፋ በደቡብ የሚገኘውን የቆጵሮስ ሪፐብሊክን ይግባኝ ይቀበላሉ።
ምጣኔ ሀብቱ በተለይ በቱሪስም ይመሰረታል፤ ቱሪስቶቹ ወይም በአየር ከቱርክ አገር፣ ወይም በመርከብ ይገባሉ። በግል ጀልባ (ያሕት) የሚገቡም አሉ። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ምርቶች የወተት ውጤቶች፣ ሎሚ፣ አረቄ፣ ዶሮ፣ ድንች ናቸው። ሕዝቡ ቱርክኛ ይናገራልና የእስልምና ተከታዮች ናቸው። ዋንኛው እስፖርት እግር ኳስ ነው። ባሕላቸው በጭፈራና በሙዚቃ፣ በሥነ ጥበብ፣ በአበሳሰል ወዘተ. እንደ ቱርክ አገር ባሕል ይመስላል።
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article ስሜን ቆጵሮስ, which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.