ፋይኮሎጂ የሚለው ቃል «የባህር አረም» የሚል ትርጓሜ ካለው (φῦκος) /ፉኮስ/ ከተሰኘ የጥንታዊ ግሪክ ቃል እና «ጥናት» የሚል ትርጓሜ ካለው (-λογία) /ሎጊያ/ ከተሰኘ የግሪክ ቃል ጥምረት የመጣ ሲሆን የዋቅላሚዎች ሳይንሳዊ ጥናት ማለት ነው። አልጎሎጂ በመባልም ይታወቅ የነበር ሲሆን ፋይኮሎጂ የሥነ-ሕይወት ዘርፍ ነው።
ዋቅላሚዎች በውሃ ስነ ምህዳር ውስጥ የመጀመሪያ ደረጃ ምርት በመሆን ያገለግላሉ። አብዛኛዎቹ ዋቅላሚዎች ውን ኑክለሳውያን, የብርሃን አስተጻምሮ የሚያካሂዱ እና እርጥበት ባለበት አካባቢ የሚኖሩ ፍጥረታት ናቸወ። ከከፍተኛ ተክሎች የሚለዩት በእውነተኛ ሥሮች፣ ግንዶች ወይም ቅጠሎች የሌላቸው በመሆኑ ነው። አበቦችን አያብቡም። ብዙ ዝርያዎች ነጠላ-ሕዋስ እና ጥቃቅን (ፋይቶፕላንክተን እና ሌሎች ደቂቅ ዋቅላሚዎችን ጨምሮ) ሲሆኑ ሌሎቹ ደግሞ በአንድ ወይም በሌላ ደረጃ ባለብዙ ህዋሳት ናቸው። ከእነዚህ ውስጥ አንዳንዶቹእንደ ከልፕ እና ሳርጋሰም ያሉ የባህር አረሞች ወደ ትልቅ መጠን ያድጋሉ ።
ፋይኮሎጂ ሰማያዊ አረንጓዴአማ ዋቅላሚዎች ወይም ሲያኖባክቴርያ በመባል የሚታወቁትን ቅድመ ኑክለሳውያን ጥናትያካትታል።በርከት ያሉ ጥቃቅን ዋቅላሚዎች እንዲሁ በላይከን ውስጥ እንደ ተደጋጋፊ አካላት በመሆን ይገኛሉ።
ፋይኮሎጂስቶች በአብዛኛው የሚያተኩሩት በለጋውሃ ወይም በውቅያኖስ ዋቅላሚዎች ላይ ሲሆን፣ በተጨማሪ ከእነዚህ ዘርፎች ውስጥ ደግሞ በባልጩት ዋቅላሚዎች ወይም ለስላሳ አካል ባላቸው ዋቅላሚዎች ላይ ሊሰሩ ይችላሉ።
የጥንት ግሪኮችም ሆኑ ሮማውያን ስለ ዋቅላሚዎች ያውቁ ነበር፣ እንደውም የጥንት ቻይናውያን አንዳንድ ዝርያዎችን እንደ ምግብ አድርገው ሲያመርቱ የነበር ቢሆንም፣ የዋቅላሚዎች ሳይንሳዊ ጥናት የተጀመረው በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መገባደጃ በ1757 በፔር ኦስቤክ አማካኝነት ፉከስ ማክሲመስ (አሁን ኤክሎኒያ ማክሲማ) ለተባለው ዝርያ ገለጻ እና ስያሜ በመስጠት ነበር።ይህን ተከትሎ እንደ ዳውሰን ተርነር እና ካርል አዶልፍ አጋርድ ባሉ ምሁራን የተሰራ ገላጭ ስራ ነበር፤ነገር ግን በዋቅላሚዎች ውስጥ ጉልህ ቡድኖችን የመፍጠር ሙከራዎች የተደረጉት በ19 ኛው ክፍለ ዘመን ማገባደጃ በጄቪ ላሞሮክስ እና በዊልያመ ሄንሪ ሃርቪ ነበር፡፡ ሃርቪ ዋቅላሚዎችን በቀለማቸው ላይ በመመስረት ወደ አራት ዋና ክፍሎች ስለመደበ በከፊል"የዘመናዊው ፋይኮሎጂ አባት" ተብሎ ተጠርቷል፡፡
በ19 ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ እና በ 20 ኛው ክፍለ ዘመን መግቢያ ላይ ነበር ፋይኮሎጂ የራሱ ችሎ እውቅና ያለው መስክ የሆነው። እንደ ፍሬድሪክ ትራውጎት ኩትዚንግ ያሉ ሰዎች ገላጭ ስራውን ቀጥለው ነበር። በጃፓን ከ 1889 ጀምሮ ኪንታሮ ኦካሙራ ስለ ጃፓን የባህር ዳርቻ ዋቅላሚዎች ዝርዝር መግለጫዎችን ብቻ ሳይሆን ስለ ስርጭታቸውም አውዳዊ ትንታኔ ሰጥቷል።
ምንም እንኳን አርኬ ግሬቪል አልጌ ብሪታኒኬን በ1830 ያሳተመ ቢሆንም፣ የመለያ ቁልፎች ዝግጅት፣ ሲስተማቲክ ኮሪሌሽን እና ሰፊ የስርጭት ካርታ ስራ የብሪታንያ የባህር ውስጥ ዋቅላሚዎች ካታሎግ በ1902 በአርነስተ ውስጥ በኤድዋርድ አርተር ሊዮኔል ባተርስ እስከታተመበት ጊዜ ድረስ አልነበረም።
ከ1899-1900, አና ዌበር-ቫን ቦሴ የደች ፋይኮሎጂ ባለሙያ የሲቦጋ ጉዞን ከተጉዋዘች በኋላ በ 1904 “ዘ ኮራሊናሲዬ ኦፍ ዘ ሲቦንጋ ኤክስፔዲሽን” የተሰኘውን ህትመት አሳትማለች።
እ.ኤ.አ. በ 1803 ዣን ፒየር ቫውቸር በዋቅላሚዎች ውስጥ ስላለው አይሶጋሚ(ጾታዊ ግንኙነት) ያሳተመው ህትመት ነበር፤ነገር ግን የዋቅላሚዎች ስርአተ እርባታ እና እድገት በስፋት መጠናት የተጀመረ በ20ኛው ክፍለዘመን መግቢያ ላይ ነበር። ፊሊክስ ዩዢን ፍሪሽ እ.ኤ.አ. በ1935 እና 1945 ያሳተማቸው የተደራጁ እትሞች ስለዋቅላሚዎች ስነቅርጽ እና ስር አተ እርባታ የታወቁ ነገሮች ተጠናቅረውባቸዋል።ይህን ተከትሎ በ1950ዎቹ በሜሪ ፓርኬ የሚመራ የአካባቢ ማረጋገጫ ዝርዝሮች ዝግጅት በ1931ዱ "ከማንክስ አልጌ" እትሟ ላይ፤እሱን ተከትሎ ደግሞ በ1953 "የብሪታንያ የባህር ዋቅላሚዎች የመጀመሪያ ደረጃ ማረጋገጫ ዝርዝር” በተሰኘው እትሟ ተሰርቷል።
ምንም እንኳን የሊሊ ኒውተን የ1931 መመሪያ መጽሃፍ ለብሪታንያ ደሴቶች ዋቅላሚዎች የመጀመሪያውን የመለያ ቁልፍ ያቀረበ ቢሆንም የእንደዚህ ዓይነቶቹ ቁልፎች መደበኛ የሆኑት ገና በ1960 ዎቹ ነበር።በ1980ዎቹ በስነ ምህዳር ላይ በአዲስ መልኩ ትኩረት መደረጉ በዋቅላሚዎች ስብስብ ላይ እና በትላልቅ እጽዋት ስብስብ ውስጥ ዋቅላሚዎች ስላላቸው ስፍራ ተጨማሪ ጥናት ተደርጓል፤ እናም አካባቢአዊ ልዩነቶችን ለማስረዳት ተጨማሪ መሳሪያ አቅርቧል።.
እጅግ የበለጸገ የባህር አረም ያላት አህጉር አውስትራሊያ ስትሆን ወደ 2,000 የሚሆኑ ዝርያዎች ያሏት።
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article ፋይኮሎጂ, which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.