ፍሪታውን የሴራሊዮን ዋና ከተማ ነው።
የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር 1,051,000 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 08°30′ ሰሜን ኬክሮስ እና 13°17′ ምዕራብ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።
ቦታው መጀመርያ በ1779 ዓ.ም. በቀድሞ ባርያ ገበያ ሥፍራ ላይ በ400 ነጻ ጥቁሮች ከአሜሪካ ተሠፈረ። በአሜሪካ ነጻነት ጦርነት ጊዜ ለእንግሊዝ መንግሥት ታማኝ ስለ ነበሩ የእንግሊዝ ጸረ-ባርነት ድርጅቶች መሬት ለዋጋቸው ሰጣቸው። መሬቱን ከዙሪያው ተምኔ ወገን ገዙ። ነገር ግን ብዙዎቹ ሠፈረኞች ከበሽታ አርፈው ፍሪታውን በ1782 ዓ.ም. ተቃጠለ።
የሲዬራ ሊዎን ድርጅት (የእንግሊዝ ጸረ-ባርነት ድርጅት) እንደገና ሙከራ አድርጎ በ1784 ዓ.ም. 1,100 ነጻ ጥቁሮች ከአሜሪካ በፍሪታውን ተሠፈሩ። 500 ነጻ ሰዎች ከጃማይካም በ1792 ዓ.ም. ደረሱ። ከ1800 እስከ 1866 ዓ.ም. ድረስ የእንግሊዝ ምዕራብ አፍሪካ መቀመጫ ነበረ።
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article ፍሪታውን, which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.