ማግና ካርታ በ1207 ዓ.ም.
የእንግሊዙ ንጉስ ጆን (ዮሐንስ) የተቀበለው የመብት ቻርተር ሰነድ ነው። ሰነዱ ለመጀመሪያ ጊዜ የረቀቀው በካንተርበሪ ሊቀ ጳጳስ ሲሆን ዋና ዓላማውም በተጠላው ንጉስ እና በአማጺ መኳንንቱ መካከል ሰላም ለማውረድ ነበር። የቤተክርስቲያንን መብት እንዲጠበቅ፣ የመኳንንቱን ያለህግ መታሰር እንዲከልከል፣ ፍትህ ሳይጓተት በፍጥነት እንዲገኝ፣ ለንጉሱ የሚደርገው ክፍያ ገደብ እንዲኖረው የሚያዘው ይህ ቻርተር በ25 መኳንንት ምክር ቤት እንዲተገበር ያዛል።
ማግና ካርታ፣ የንጉሱ ሥልጣን ከህግ በታች እንደሆነ እና ነጻ ሰዎች ያላቸውን መብት በማጽደቁ፣ በእንግሊዝና በኋላም በአሜሪካ አገሮች ለተገኘው ግለሰባዊ ነጻነት መሰረት የጣለ ሰነድ ነው።
ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article ማግና ካርታ, which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.