ክሪስቶፎር ኮሎምበስ በሰሜን ምዕራብ ጣሊያን፣ ጀኖዋ ከተማ በ1451 እ.ኤ.አ.
የኮሎምበስ የጉዞ አላማ ቻይናንና ህንድን ከአውሮጳ ጋር የሚያገናኝ መስመር በአትላንቲክ ውቅያኖስ ላይ በማግኘት የቅመማ ቅመም እና ወርቅ ንግድ ለስፔን ነገስታት በሚያመች መልኩ እንዲካሄድ ማድርግ ነበር። በጊዜው ይህ ሃሳብ እንግዳ ነበር ምክንያቱም ቻይናና ህንድ ከአውሮጳ በስተምስራቅ እንጂ በስተ ምዕራብ አይገኙምና።
ኮሎምበስ፣ መሬት ድቡልቡል እንደሆነች ያውቅ ነበር፤ በተረፈም ከማርኮ ፖሎ መጻሕፍት እንደተረዳ ከቻይና ምስራቅ ውቅያኖስ እንዳለ ያውቅ ነበር። ይህ ውቅያኖስ የአትላንቲክ ውቅያኖስ ነው ብሎ ኮሎምበስ በስህተት በመደምደም ነበር ጉዞ የጀመረው። ስለሆነም በአትላንቲክ ላይ ከተጓዘ በኋላ ያገኘውን የመጀመሪያውን ደረቅ መሬት ምስራቃዊ ህንድ በማለት ሰይሞታል፣ ይሄውም ባሃማስ ደሴት ሲሆን የአሜሪካ ክፍል ነው። ኮሎምበስ፣ ከዚህ በኋላ ወደ ባሃማስ፣ አሜሪካ አራት ጊዜ ጉዞ አድርጓል። በነዚህ ሁሉ ጊዜ የኮሎምበስ እምነት አዲስ አህጉር እንዳገኘ ሳይሆን ህንድን ከምዕራብ በኩል እንደደርሰበት ነበር።
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article ክሪስቶፎር ኮሎምበስ, which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.