አለቃ ኪዳነወልድ ክፍሌ (ከ፲፰፻፷፬ እስከ ፲፱፻፴፯ ዓ.ም.)
አለቃ ኪዳነወልድ ክፍሌ በሸዋ ክፍለ ሀገር በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ በ፲፰፻፷፬ ዓ.ም. ተወለዱ። ለትምህርት ሲደርሱ በአካባቢያቸው የነበረውን የአገራቸውን ትምህርት ተማሩ። በኋላም ወደ ጎንደር ተጉዘው የመጻሕፍትን ትርጓሜ አጠኑ። በጊዜው የነበራቸው የቀለም አቀባበል፣ የሚስጥር መመራመርና መራቀቅ በጉባኤው ላይ «የቀለም ቀንድ» የሚል ቅጽል ተሰጣቸው።ማናቸው ማናቸው
አለቃ ኪዳነወልድ ከግዕዝና አማርኛ ሌላ ዐረብኛ፣ ዕብራይስጥ፣ ላቲን፣ ሌሎችንም ቋንቋዎች አጠናቅቀው ያውቁ ነበር ። አለቃ ኪዳነወልድ በእየሩሳሌም ለ፳፪ ዓመት ተቀምጠዋል ። በዚህም ወቅት ብሉይና ሐዲስ በሦስት ቋንቋ ጠንቅቀው አመሳክረው ተርጕመዋል ። ኪዳነወልድ ክፍሌ በ፲፱፻፳፮ ዓ.ም. የመጀመሪያውን መዝገበ ፊደል አውጥተው ከልዩልዩ ቋንቋዎች ጋር በማመሳከር አሳትመዋል ። የኢትዮጵያ ፊደል አመጣጡንና ባህሉን በውል አስተባብረው በማቅረባቸውም በጊዜው ተቋቁመው ለነበሩት ትምህርት ቤቶች መመሪያና መማሪያ ለመሆን በቅተዋል ። ቀጥለውም ትንሽ አማርኛ ፊደል ከአረብና ከዕብራይስጥ አቆራኝተው አሳትመዋል ።
አለቃ ኪዳነወልድ በተለያየ ዘይቤ ያቀርቧቸው የነበሩት ግጥሞች ለትውልድ ታላቅ ጥቅም ይሰጣሉ ተብለው የሚገመቱ ናቸው ። እንዲያውም ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪቃ የብዙ ሺሕ ዘመናት ነጻ አገር ባለፊደልና ባለቋንቋ የሆነች እሷ ብቻ ስለሆነች ትውልድ ያገሩን ትምህርት በመጀመሪያ እንዲማር ያካሂዱት የነበረው ቅስቀሳ በቀላሉ የሚታይ አይደለም ። በዓለም ስማቸው የገነነ የሥነ ጥበብ፣ የኪነ ጥበብ ፣ የጽሑፍ ባለአጉዛዎች የሚደነቁባቸው በራሳቸው ቋንቋ ጽፈው ለዓለም የአቀረቧቸው ሥራዎች ናቸው ይላሉ ።
አለቃ ኪዳነወልድ ለኢትዮጵያ ባላቸው ዐቅም በብሔራዊ ስሜት ተነሳስተው ለታሪክ የሚቀርቡ በርከት ያሉ መጻሕፍት ጽፈው አሳትመዋል ። በተለይም ከዘጠኝ መቶ ገጾች በላይ የሆነው «የሰዋሰው መጽሐፍ» ታላቅ እንደሆነ ይነገራል ። አለቃ ኪዳነወልድ ለኢትዮጵያ ሥነ ጽሑፍ ታላቅ አስተዋፅኦ ያደረጉ ሰው ነበሩ ።
አለቃ ኪዳነወልድ ክፍሌ በተወለዱ በ ፸፪ ዓመታቸው ፤ ሰኔ ፳፬ ቀን ፲፱፻፴፮ ዓመተ ምሕረት ዐርፈው ደብረ ሊባኖስ ተቀበሩ።[2]
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article ኪዳነ ወልድ ክፍሌ, which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.