ግዕዝ

ግዕዝ ፡ በአፍሪካ ቀንድ ፡ በኢትዮጵያና ፡ በኤርትራ ፡ በጥንት ፡ የተመሠረተና ፡ ሲያገለግል ፡ የቆየ ፡ ቋንቋ ነው። የግዕዝ ፡ አመጣጥ ፡ በግምት ፡ የዛሬ ፡ ፫ ፡ ሺህ ፡ ዓመት ፡ ከየመን ፡ እና ፡ ደቡብ ፡ አረቢያ ፡ በመነሣትና ፡ ቀይ ፡ ባሕርን ፡ በመሻገር ፡ በኤርትራ ፡ እና፡ ሰሜን ፡ ኢትዮጵያ ፡ ውስጥ ፡ ከሰፈሩ ፡ የተለያዩ ፡ የሳባውያን ፡ ነገዶች ፡ ቋንቋና ፡ በጊዜው ፡ ሰሜን ፡ ኢትዮጵያ ፡ ይነገሩ ፡ በነበሩ ፡ ቋንቋዎች ፡ ዘገምተኛ ፡ ውኅደት ፡ ነው። በአክሱም ፡ መንግሥትና ፡ በኢትዮጵያ ፡ መንግሥት ፡ መደበኛ ፡ ቋንቋ ፡ ነበር።

ግዕዝ
ኦሪት ፡ ዘፍጥረት ፡ ፳፱ ፡ በግዕዝ ፡ መጽሐፍ ፡ ቅዱስ

ግዕዝ ፡ ከአማርኛና ፡ ሌሎች ፡ ኢትዮ-ሴማዊ ፡ ቋንቋዎች ፡ ጋር ፡ ሲወዳደር ፡ «ንጹሕ» ፡ ሴማዊ ፡ ቋንቋ ፡ ነው። ግዕዝ ፡ እስከ ፡ ፲ኛው ፡ ክፍለ-ዘመን ፡ መጀመሪያ ፡ ድረስ ፡ ዋነኛ ፡ የመግባቢያ ፡ ቋንቋና ፡ ልሳነ ፡ ንጉሥ ፡ ነበር። ከ ፲፫ኛው ፡ ክፍለ ፡ ዘመን ፡ ጀምሮ ፡ ግን ፡ ሙሉ ፡ በሙሉ ፡ መነገር ፡ አቁሞ ፡ በሰሜን ፡ ኢትዮጵያ ፡ በትግርኛ ፡ እንዲሁም ፡ በማዕከላዊው ፡ ክፍል ፡ ደግሞ ፡ በአማርኛ ፡ ተተካ። ዛሬ ፡ በኢትዮጵያ ፡ ኦርቶዶክስ ፡ ተዋሕዶ ፡ ቤተክርስቲያን ፡ ሥነ-ስርዓት ፡ እንዲሁም ፡ በኤርትራ ፡ ኦርቶዶክስ ፡ ተዋሕዶ ፡ ቤተክርስቲያን ፣ በኢትዮጵያ ፡ ካቶሊክ ፡ ቤተክርስቲያን እና ፡ በቤተ-እስራኤል ፡ ሥነ-ስርዓቶች ፡ ይሰማል። በሰሜን፡ ኤርትራ ፡ የሚገኘ ፡ ትግረ ፡ የሚባል ፡ ቋንቋ ፡ ከሁላቸዉ፡ የሰሜን ፡ኢትዮጵያ ፡ቋንቋዎች፡ ለግእዝ ፡ በቅርብ ፡ ይዛመዳል ፡ እና። ትግረ ፡ ፸ በመቶ ፡ ግእዝ ፡ ነዉ ፡ እና ፡ በመቀጠል ፡ ትግርኛ ፡ እና ኣማርኛ።

ቋንቋው ፡ የሴማዊ ፡ ቋንቋዎች ፡ አባል ፡ እየሆነ ፡ በደቡብ ፡ ሴማዊ ፡ ቅርንጫፍ ፡ ውስጥ ፡ ይካተታል። ደቡብ ፡ ሴማዊ ፡ በመባሉ ፡ ግዕዝ ፡ የሣባ ፡ ቋንቋ ፡ ቅርብ ፡ ዘመድ ፡ ነው። ግዕዝ ፡ የተጻፈው ፡ በግዕዝ ፡ ፊደል ፡ አቡጊዳ ፡ ነው። ይህም ፡ ፊደል ፡ ደግሞ ፡ ዛሬ ፡ ለአማርኛ ፣ ለትግርኛ ፡ እና ፡ ለሌሎችም ፡ ቋንቋዎች ፡ ይጠቀማል። በመላውም ፡ የአፍሪቃ ፡ አህጉር ፡ ውስጥ ፡ የመጀመሪያውና ፡ ብቸኛ ፡ አፍሪቃዊ ፡ የራሱን ፡ ፊደላት ፡ የያዘ ፡ ቋንቋ ፡ ሲሆን ፣ በዓለምም ፡ ላይ ፡ ዋናና ፡ የስልጣኔ ፡ አራማጅ ፡ ከሚባሉት ፡ ቋንቋዎች ፡ አንዱ ፡ ነው።

በግዕዝ ፡ ጽሕፈት ፡ ፳፮ ፡ ፊደላት ፡ ብቻ ፡ ይጠቀሙ ፡ ነበር ፤ እነርሱም፦

ሀ ፣ ለ ፣ ሐ ፣ መ ፣ ሠ ፣ ረ ፣ ሰ ፣ ቀ ፣ በ ፣ ተ ፣ ኀ ፣ ነ ፣ አ ፣ ከ ፣ ወ ፣ ዐ ፣ ዘ ፣ የ ፣ ደ ፣ ገ ፣ ጠ ፣ ጰ ፣ ጸ ፣ ፀ ፣ ፈ ፣ ፐ

ናቸው።

ሊቁ ፡ ሪቻርድ ፓንኩርስት ፡ እንደሚጽፍ ፣ አንድ ፡ ተማሪ ፡ በመጀመርያው ፡ አመት ፡ ፊደሉን ፡ ከተማረ ፡ በኋለ ፣ በሚከተለው ፡ አመት ፡ መጀመሪያይቱ ፡ የሐዋርያው ፡ የዮሐንስ ፡ መልእክትን ፡ ከአዲስ ፡ ኪዳን ፡ በግዕዝ ፡ ከትዝታ ፡ ለመጻፍ ፡ መማር ፡ ነበረበት። በሦስተኛው ፡ ደረጃ ፡ የሐዋርያት ፡ ሥራ ፡ በአራተኛውም ፡ መዝሙረ ፡ ዳዊት ፡ በግዕዝ ፡ ማስታወስ ፡ ነበረበት። ይህንን ፡ ከጨረሰ ፡ ታላቅ ፡ ግብዣ ፡ ይደረግና ፡ ልጁ ፡ ጸሐፊ ፡ ይሆን ፡ ነበር።

በብሪቲሽ ፡ ቤተ-መጻሕፍት ፡ (የእንግሊዝ ፡ አገር ፡ ብሔራዊ ፡ ቤተ-መጻሕፍት) ፡ ውስጥ ፡ ፰፻ ፡ የሚያሕሉ ፡ የድሮ ፡ ግዕዝ ፡ ብራናዎች ፡ አሉ።

በኢ.ኦ.ተ.ቤ. ፡ ትምህርቶች ፡ ዘንድ ፣ ግዕዝ ፡ የአዳምና ፡ የሕይዋን ፡ ቋንቋ ፡ ነበር። ፊደሉን ፡ የፈጠረው ፡ ከማየ አይኅ ፡ አስቀድሞ ፡ የሴት ፡ ልጅ ፡ ሄኖስ ፡ ነበረ። ከባቢሎን ፡ ግንብ ፡ ውድቀት ፡ በኳላ ፣ ከአርፋክስድ ፡ ወገን ፡ የዮቅጣን ፡ ልጆች ፡ ቋንቋውን ፡ እንደ ፡ ጠበቁት ፡ ይባላል። የዮቅጣን ፡ ልጅ ፡ ሣባ ፡ ነገዶች ፡ ከዚያ ፡ ቀይ ፡ ባሕርን ፡ አሻግረው ፡ ወደ ፡ ዛሬው ፡ ኢትዮጵያ ፡ ያስገቡት ፡ ይታመናል። እንዲሁም ፡ ካዕብ ፡ እስከ ፡ ሳብዕ ፡ (አናባቢዎችን ፡ ለመለየት) ፡ ወደ ፡ ፊደል ፡ የተጨመረበት ፡ ወቅት ፡ በንጉሥ ፡ ኤዛና ፡ ዘመን ፡ እንደ ፡ ነበር ፡ ይባላል።

ጀመረ

ግዕዝ 
አንድ ፡ የግዕዝ ፡ ሰነድ ፡ ውዳሴ ፡ ማርያም (፲፰፻፷፯ (1867) ዓ.ም. ፡ ገደማ)

ግሥ

  • ግዕዝ - አማርኛ
  • ነገረ - ነገረ(ተናገረ)
  • ነገረት - ነገረች
  • ነገርከ - ነገርክ
  • ነገርኪ - ነገርሽ
  • ነገርኩ - ነገርሁ
  • ነገሩ - ነገሩ
  • ነገራ - ነገሩ (ሴ)
  • ነገርክሙ - ነገራችሁ
  • ነገርክን - ነገራችሁ(ሴ0
  • ነገርነ - ነገርን
  • ይነግር - ይነግራል
  • ትነግር - ትነግራለች
  • ትነግር - ትነግራለህ
  • ትነግሪ - ትነግሪያለሽ
  • እነግር - እነግራለሁ
  • ይነግሩ - ይነግራሉ
  • ይነግራ - ይነግራሉ
  • ትነግሩ - ትነግራላችሁ
  • ትነግራ - ትነግራላችሁ(ቅ.ሴ)
  • ንነግር - እንነግራለን
  • የእግዚአብሔር ስጦታ

የቱ

ምሳሌ

«ቃለ ፡ በረከት ፡ ዘሄኖክ ፡ ዘከመ ፡ ባረከ ፡ ኅሩያነ ፡ ወጻድቃነ ፡ እለ፡ ሀለው፡ ይኩኑ ፡ በዕለተ ፡ ምንዳቤ ፡ ለአሰስሎ ፡ ኲሉ ፡ እኩያን ፡ ወረሲዓን።» (መጽሐፈ ፡ ሄኖክ ፩ ፡ ፩)

ሄኖክ ፡ መጀመርያ ፡ ቃሎች ፡ በጽሕፈት ፡ በግዕዝ ፡ የጻፈ ፡ እንደ ፡ ነበር ፡ ስለሚባል ፣ ይህ ፡ ቃል ፡ በማንኛውም ፡ የሰው ፡ ልጅ ፡ ቋንቋ ፡ ከሁሉ ፡ አስቀድሞ ፡ የተጻፈ ፡ መሆኑ ፡ በብዙዎች ፡ የኢትዮጵያ ፡ ሊቃውንት ፡ ይታመናል።

ደግሞ ፡

  • ኣበራ ፡ ሞላ - ከቅርብ ፡ ጊዜ ፡ ወዲህም ፡ እዚህ ፡ ገጽ ፡ ላይ ፡ እንደሚታየው ፡ ግዕዝን ፡ በኮምፕዩተር ፡ መጻፍ ፡ ተችሏል።

የውጭ ፡ መያያዣዎች

ማጣቀሻዎች

Tags:

ግዕዝ ጀመረግዕዝ ምሳሌግዕዝ ደግሞ ፡ግዕዝ የውጭ ፡ መያያዣዎችግዕዝ ማጣቀሻዎችግዕዝቀይ ባሕርአክሱም መንግሥትኢትዮጵያኤርትራየመን (አገር)

🔥 Trending searches on Wiki አማርኛ:

ማርያምሰላማዊ ውቅያኖስሰንሰልስዊዘርላንድአበሻ ስምየኢትዮጵያ የ5 ሺ ዓመት ታሪክ ከኖኅ እስከ ኢህአዴግሆሣዕና (ከተማ)የተባበሩት ግዛቶችአፈ፡ታሪክአዳልንግሥት ኤልሣቤጥ ዳግማዊትዛጔ ሥርወ-መንግሥትፋሲል ግምብየኢትዮጵያ ታሪክ፡ ሐሪ አትከንስግብርስልጆገዳ ሥርዓት አራማጅ ፓርቲአክሱም ጽዮንኩናማጸሎተ ምናሴቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊውቅያኖስምግብደመቀ መኮንንባኃኢ እምነትሰንበትፍቅር በአማርኛየመን (አገር)ጌዴኦየሥነ፡ልቡና ትምህርትየሰው ልጅትግራይ ክልልዩ ቱብመሬትየማርቆስ ወንጌልማህፈድየኮንሶ ባህላዊ የእርከን ስራቆለጥየሰው ልጅ ጥናትታሪክሥነ ምግባርኤርትራየወታደሮች መዝሙርኮሶ በሽታትምህርትንግሥት ዘውዲቱየኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙርቶቶሮቡርኪና ፋሶጂጂመዝሙረ ዳዊትጥርኝቃል (የቋንቋ አካል)ጥሩነሽ ዲባባአማራ (ክልል)ፋሲለደስየኢትዮጵያ ቡናአማርኛ ልብ ወለድ መፃህፍትጠጣር ጂዎሜትሪስምጎንደር ከተማጉንዳንሊጋባአብዲሳ አጋየግሪክ አልፋቤትካናዳዳግማዊ ምኒልክጋምቤላ ሕዝቦች ክልልማይልፋርስየጥንተ ንጥር ጥናትርዕዮተ ዓለምየደም ቧንቧ🡆 More