አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በአዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ የመጀመሪያውና ትልቁ የመንግሥት የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ነው። አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ስምነት የኢትዮጵያን የትምህርት ፋናንና ዕርምጃን እንዲያሳይ ታኅሣሥ ፱ ቀን ፲፱፻፶፬ ዓ.ም.
ከመመረቁ በፊት፣ መሠረቱ በንጉሠ ነገሥቱ ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፵፪ ዓ.ም. ተጣለ። ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ አዲስ አበባ በመባል ይታወቅ ነበር፤ በኋላም የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርስቲ የሚል ስያሜ የነበረው ሲሆን የዘውዳዊው መንግሥት ሥርዓት ካከተመ በኋላ የተመሠረተው ወታደራዊ መንግሥት አሁን በሚጠራበት ስሙ ሰይሞታል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዋና አስተዳደሩን ሰድስት ኪሎ በሚገኘው በዋናው ግቢ ያደረገ ሲሆን በአምስት ኪሎ (የቴክኖሎጂ ፋኩለቲ-ሰሜን)፣ በአራት ኪሎ የሳይንስ ፋኩልቲ፣ በስድስት ኪሎ (የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ፋኩልቲ እንዲሁም የኢንፎርማቲክስ ፋኩልቲ)፣ በጥቁር አንበሳ (የህክምና ፋኩልቲ ) በልደታ (የቴክኖሎጂ ፋኩለቲ-ደቡብ)፣ በብሔራዊ (የአዲስ አበባ ንግድ ስራ ኮሌጅ)፣ በሚኒሊክ (የያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት)፣ የጥርስ ህክምና ትምህርት ቤት፣ እንዲሁም በደብረዘይት ከተማ የእንሰሳት ህክምና ፋኩልቲን ያስተዳድራል። አዲስ አበባ በስሩ የሚከተሉትን ፋኩልቲዎች እና ኢንስቲቲዩቶች ይዟል፦
የኢንፎርማቲክስ ፋኩልቲ በአዲስ መልክ የተመሠረተው በ1994 ዓ.ም. ሲሆን ቀድሞ ሲሳ (ስኩል ኦፍ ኢንፎርሜሽን ስተዲስ ፎር አፍሪካ) በመባል ይታወቅ ነበር። በአሁኑ ሰዓት የኢንፎርማቲክስ ፋኩልቲ በስሩ የኢንፎርሜሽን ሳይንስ ትምህርት ክፍልን እና የኮምፒዩተር ሳይንስ ትምርት ክፍልን ይዞአል። ሁለቱም የትምህርት ክፍሎች የባችለርና የማስተርስ ፕሮግራሞች አሉዋቸው።
ኢንፎርሜሽን ሳይንስ ማለት ኢንፎርሜሽን ሳይንስ ማለት ነው?
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.