- ኅዳር ፳፩ - ክቡር ደጃዝማች ኃብተ ሥላሴ በላይነህ በአሌልቱ ሜዳ ላይ ሦስት ቀን ሙሉ ጦርነት አደረጉ፣ ከጠላት በኩል የኢጣሊያ ፋሽስቶች ፺፮ መኮንኖችና ወታደሮች ተግድለዋል።
- ታኅሣሥ ፩ - በብሪታንያ በንጉሡ የፍቅረኛቸውን ምርጫ ምክንያት በተከሰተው ቀውስ፥ ንጉሥ ኤድዋርድ ስምንተኛ ሥልጣናቸውንና ዘውዳቸውን መልቀቅ የሚያስችላቸውን ህግና ስምምነት ፈረሙ።
- ታኅሣሥ ፲፱ - በባሌ ጠቅላይ ግዛት ውስጥ ቡላንቾ (አርበጎና) የሚባል ሥፍራ ላይ ሙሴ ቀስተኛና ራስ ደስታ ዳምጠው ተገናኝተው ለሁለት ሰዓት ያህል ተወያዩ።
- ጥር ፲፪ - የፋሺስት ኢጣልያ የጦር ዓለቃ ማርሻል ግራትዚያኒ በራሡ መሪነት የራስ ደስታ ዳምጠውን ሠራዊት በሲዳሞ እና የደጃዝማች ገብረ ማርያምን ሠራዊት በባሌ ለመውጋት ዘመተ።
- ጥር ፲፫ - ጃንሆይ በእንግሊዝ በስደት ሆነው ወደ ኢየሩሳሌም ወደ እጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ (በኋላ አቡነ ባስልዮስ) ጽላቱ ለምስካዬ ኅዙናን መድኅኔ ዓለም ቤተክርስቲያን እንዲልኩላቸው ደብዳቤ ላኩ።
- ጥር ፳፯ - የኢትዮጵያ መላክተኛ በብሪታኒያ አዛዥ ወርቅነህ የሹመት ማስረጃቸውን ለንጉሡ ኤድዋርድ 8ኛ አቅርበዋል።
- የካቲት ፲፪ - ግራዚያኒን ለመግደል በተደረገው ሙከራ የስንዱ ገብሩ ወንድም መሸሻ ገብሩ አሉበት በመባል ይታሰሱ ስለነበር ሰንዱ ወንድማቸውን ከአደጋ ለማዳን ሲሞክሩ በድጋሚ በፋሺስቶች እጅ ወደቁ። ጸሐፊው ተክለጻድቅ መኩርያ ደግሞ በዚህ ቀን ተማረኩ።
- የካቲት ፲፭ - ራስ ደስታ ቡታጅራ አካባቢ ላይ በትግራይ ተውላጅ ደጃዝማች ተክሉ መሸሻ ተያዙ።
- የካቲት ፲፮ - በግራትዚያኒ የሚመራ የፋሺስት ኢጣልያ ሠራዊት በዝዋይ አካባቢ የጦር አዝማቾቹን የራስ ደስታ ዳምጠውን እና የደጃዝማች በየነ መርዕድን አርበኞች ድል አደረጉ። ሁለቱም ኢትዮጵያውያን አዝማቾች ሕይወታቸውን በዚህ ዕለት ሰዉ። ኢጣሊያውያኑ ራስ ደስታን ከያዟቸው በኋላ በጥይት ደበደቧቸው።
- መጋቢት ፪ - በልሚ ወቼ ሞሹ የኢትዮጵያ አርበኞችና የፋሺስት ኢጣሊያ ወገኖች ጦር ውጊያ
- ሚያዝያ ፳፫ - አርበኛው ደጃዝማች ኪዳኔ ወልደመድኅን ተማም ከሚባለው ሥፍራ ላይ በጠላት እጅ ተማረኩ።
- ሰኔ ፲ - አርበኛው በላይ ዘለቀ በዋሻ ተከበበ።
ገና ያልተወሰነ ቀን፦
ልደት
ዕለተ ሞት
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article 1929, which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.