የትግራይ ሽግግር መንግሥት

የትግራይ ሽግግር መንግስት በትግራይ ክልል ስልጣን ላይ በነበረበት ጊዜ በህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) እና በፌደራል መንግሥት መካከል በተፈጠረው ግጭት ምክኒያት በኢትዮጵያ ፌደሬሽን ም / ቤት በይፋ የታወጀ አስተዳደር ነው።

ዳራ

በመጋቢት 2018 (እ.ኤ.አ.) የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በሌተናል ኮ / ል አብይ አህመድ ለሚመራው መንግስት ስልጣኑን በመስጠት ዘላቂ ሰላም እና ዴሞክራሲን ለማምጣት የታቀደውን ማሻሻያ በመደገፍ ስልጣናቸውን ለቀቁ። አብይ ሁሉንም የክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች በአንድ የተማከለ የፖለቲካ ፓርቲ ውስጥ ለማገናኘት ሞክሯል ፡፡ በኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) አውራ ፓርቲ የሆነው ህወሃት ፈቃደኛ ባለመሆኑ እና የብልጽግና ፓርቲው ሌሎች ሶስት የኢህአዴግ አባል ፓርቲዎች ውህደት ሆኖ ተፈጥሯል። በ2020 ኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክኒያት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለነሐሴ ወር 2020 የታቀደውን የፌዴራል ምርጫ በፌዴሬሽን ምከር ቤት ውሳኔ መሰረት ከኮሮና ስርጭት መቀነስ በኋላ ከስድስት ወይም ዘጣኝ ወር ጊዜ ዝግጅት በኋላ እንድደረግ ላልተወሰነ ጊዜ መርጫውን አስተላልፏል። ነገር ግን የፌዴሬሽን ምክር ቤት በመቃወም የትግራይን ክልል ምርጫ ለማካሄድ የራሱ የሆነ የክልል ምርጫ ቦርድ አቋቋመ። ይህንን ተከትሎ የትግራይ ክልላዊ ምርጫ የተካሄደው መስከረም 9 ቀን 2020 (እ.አ.አ.) ሲሆን ህወሓት ሙሉ መቀመጫ አሸንፍለውም ብሏል። 98.2% ያሸነፈው ህወሃት ነበር።

እ.ኤ.አ. ጥቅምት 5 ቀን 2020 የትግራይ ክልል መንግሥት ከፌደራል መንግስት ስር ያሉ ባለስልጣናት ስልጣናቸውን እንዲለቁ እና ወደ ትግራዩ መንግስት እንዲቀላቀሉ አሳስበዋል፤ ይህ ተከትሎ አብዛኞቹ የትግራይ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ስልጣናቸውን ለቀዋል። እ.ኤ.አ. ጥቅምት 7 ቀን 2020 የፌደራሉ መንግስት ከትግራይ ክልል ምክር ቤት እና ከክልሉ ከፍተኛ የስራ አስፈፃሚ አካል ጋር ያለውን ማንኛውንም ግንኙነት ለማቆም ወስነ፣ የፌዴሬሽን ምከር ቤት ለክልሉ የበጀት ድጎማዎችን አቋርጧል ፣ ሁሉም የፌዴራል ተቋማት ደብዳቤዎችን እና መረጃዎችን ወደ ትግራይ ከፍተኛ የሥራ አስፈፃሚ አካላት እንዳይልኩ ወይም ለተቋሞቻቸው ድጋፍ እንዳያደርጉ አግዶ ክልሉ በአገር አቀፍ መድረኮች እንዳይሳተፍም ውሳኔ አሳለፈ። የትግራይ መንግስትም ይህንን በክልሉ ላይ ጦርነት የማወጅ መግለጫ አድርጎ ገልፆታል።

እ.ኤ.አ. በጥቅምት 2020 በፌደራል እና በትግራይ ባለስልጣናት መካከል የተፈጠረው ግጭት ወታደራዊ ግጭት ሆኖ የፌደራል ኃይሎች እስከ ህዳር 2020 መጨረሻ ድረስ ባደረጉት "ሕግ የማሰከበር ዘመቻ" የክልሉን ዋና ከተማ መቐለን ተቆጣጥረዋል።

ሕገ-መንግስታዊ አውድ

የ1995 ቱ ሕገ መንግሥት በአንቀጽ 39 ንኡስ አንቀጽ 1 ላይ “ማንኛውም የኢትዮጵያ ብሔር ፣ ብሔረሰብ ፣ ሕዝብ የራሱን ዕድል በራሱ የመወሰን እስከመገንጠል ያለው መብቱ በማናቸውም መልኩ ያለገደብ የተጠበቀ ነው” ይላል።

በአንቀፅ 62 ንኡስ አንቀጽ 9 የ1995 ቱ ሕገ መንግሥት ለፌዴሬሽን ምከር ቤት “ማንኛውም ክልል ይህን ህገ መንግሥት በመጣስ ህገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን አደጋ ላይ የጣለ እንደሆነ የፌዴራሉ መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ” የማዘዝ ስልጣን ሰጥቶታል።

የሽግግር መንግሥት ፍጥረት

ጠ / ሚ አብይ አህመድ በመቀሌ አካባቢ ሰፍሮ የነበረው የኢትዮጵያ ብሄራዊ መከላከያ ሰራዊት በትግራይ ክልል ልዩ ሀይል ጥቃት መሰንዘሩን ህዳር 4 ቀን 2020 ለኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ገልፀዋል ፡ ይህንን ተከትሎም የኢትዮጵያ መንግስት የህግ የበላይነትን ለማስመለስ ያለመ ነው ሲል የገለጸውን እርምጃ በመጀመር በትግራይ ክልል ውስጥ ለስድስት ወራት የሚቆይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማውጣት የክልሉን ገዥ አነሳ፤ ከዚያ የፌዴሬሽን ምከር ቤት መንግሥት በትግራይ ክልል ጣልቃ እንዲገባ ፈቅዶ የትግራይ የሽግግር መንግሥት አቋቋመ።

አመራር እና መዋቅር

እንደ ጥቅምት 21፣ 2020 (እ.ኤ.አ) የመንግሥት መግለጫ፣ ዶ/ር ሙሉ ነጋ የትግራይ የሽግግር መንግሥት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆኖ ተሹመዋል።

እንደ ጥቅምት 28፣ 2020 (እ.ኤ.አ) የአስተዳደሩ አወቃቀር የሚመራው በአምስት ሰዎች ነው። ቦርከና የተባለ የኢትዮጵያ ዜና ጠንቃሪ ዌብሳይት በጥቅምት ወር ማገባደጃ እንደገለጸው የሽግግር መንገስቱን የሚመሩት ትግራዋይ ብቻ ይሆናሉ።

የሽግግር መንግስቱ አወቃቀር በዲሴምበር 2020 ተጠናቆ በፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በሚፀድቅ ቻርተር እንደሚተላለፍ ዶ/ር ሙሉ ነጋ ገልፀዋል። እስከ ህዳር 28 ድረስ ዕቅዱ በክልል ደረጃ እና በዞን ደረጃ አመራር እንዲለወጥ የታቀደ ሲሆን “ የወረዳና የቀበሌ አስተዳደሮችን ሙሉ በሙሉ ጠብቆ ማቆየት” የሚል ነበር፤ “ተቋማትን ለመምራት የተሾሙ ባለሥልጣናትን መምረጥ” ውስጥ የሕዝብ ምክክርና የሕዝብ ተሳትፎ ታቅዶ ነበር።

እ.ኤ.አ. ታህሳስ 15 ቀን 2020 ዓረና ትግራይ ፣ የትግራይ ዴሞክራቲክ ፓርቲ እና አሲምባ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ( አዴፓ ) ጨምሮ የትግራይ ተቃዋሚ ፓርቲዎች አባላት “በክልሉ ካቢኔ ውስጥ የአመራር ቦታዎች እና በተለያዩ የከፍተኛ ደረጃ ቦታዎች እንደሚሾሙ ሙሉ አስታውቋል፤ የክልል አስተዳደር " በዚህ መሠረት የአረና ትግራይ ሊቀመንበር አበራ ደስታ የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሀላፊ አድርጎ ሾመዋል።

በታህሳስ 16 ቀን 2020 የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ መካኒካል ኢንጂነሪንግ ትምህርት ክፍል መምህር አሰፋ በቀለ በክልሉ የሽግግር መንግስት የመንገድ እና ትራንስፖርት ቢሮ ሀላፊ ሆነው ተሾሙ።

ስልጣናት

ሙሉ ነጋ የሽግግር አስተዳደሩ አራት ዋና ዋና ስልጣን እንደሚኖሩት ገልፀዋል ፡፡

  • የክልል አስፈፃሚ ተቋማትን እንደገና መፍጠር፤
  • በሕዝብ ምክክር የሚመሩ የክልል እና የዞን አመራሮችን መሾም እንጂ የወረዳ እና የቀበሌ አመራሮችን አለመሾም፤
  • "ህግና ስርዓትን ማረጋገጥ"፤
  • የ 2021 የኢትዮጵያ አጠቃላይ ምርጫ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተደነገገው መሠረት ማካሄድ፤

አስተዳደሩም እንዲሁ በፌዴራል መንግሥት የተሰጣቸውን ሥራዎች “በንቃት [ተግባራዊ ለማድረግ]” ሥልጣን ተሰጥቶታል ፡፡

የተገለሉ ስልጣናት

እ.ኤ.አ ጥቅምት 28 ቀን 2020 በ “ራያ ፣ ጠለምትና ወልቃይት አከባቢዎች” በታሪካዊ ምክንያቶች የሚጠበቀው የመሬት ይገባኛል ጥያቄ አለመግባባቶች ከሽግግር አስተዳደሩ ከታቀዱት ኃይሎች እንዲገለሉ ተደርጓል።

የግዛት ቁጥጥር

ምዕራባዊ ዞን

ከኖቬምበር 23 ቀን 2020 ጀምሮ በምዕራባዊ ዞን (ምዕራባዊ ትግራይ) ከቁጥጥር ስር የሆኑ የትግራይ ከተማ ሁመራ ከአማራ ክልል በተውጣጡ ባለስልጣናት እና የፀጥታ ኃይሎች ይተዳደር ነበር፤ እንደ ሁመራ እና ጎሹ ስደተኞች መሠረት ፣ ፋኖ የተባለ የአማራ የወጣት ቡድን የሁመራ ፍርድ ቤት መቆጣጠሩን አረጋግጦ ነበር።

ሰሜን ምዕራባዊ ዞን

ታህሳስ 2፣ 2020 (እ.ኤ.አ) ላይ፣ ዶ/ር ሙሉ እንዳሉት በሰሜን ምዕራብ ትግራይ ዞን ስር የሚገኝ ሽሬ እንደ ስላሴ ወረዳ ውስጥ የሚገኙ ቀበሊያት ነዋሪዎች፣ እያንዳንዱ ቀበሌ 20 ተወካይ ያደራጁ ሲሆን እነዚህም አንድ ላይ 25 የወረዳ ምክር ቤት አባላትን ምክር ቤቱ አምስት አባላቱን ካቢኔ አድርጎም ሾሟል። የወረዳው አስተዳዳሪም መመረጣቸውን ዶ/ር ሙሉ ጨምሮ ገልፀዋል።

ታህሳስ 15 ቀን ስማቸው ያልተጠቀሰ የመቀሌ ከንቲባ መሾም በሙሉ ተገለፀ ፡ እ.ኤ.አ. ታህሳስ 16 ቀን 2020 (እ.አ.አ.) እ.ኤ.አ. የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ ኦፊሴላዊ የፌስ ቡክ ገጽን የጠቀሰው የኢትዮጵያ ቃና ቴሌቪዥን አዲሱ ከንቲባ የመቀሌ ዩኒቨርስቲ መምህርና የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አታኽልቲ ኃይለስላሴ ናቸው።

ደቡባዊ ዞን

እ.ኤ.አ. ታህሳስ 16 ቀን 2020 የትግራይ የሽግግር መንግስት ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት ዶ/ር ሙሉ ሚሊዮን አበራን የደቡባዊ ዞን ዋና ስራ አስፈፃሚ አድርገው ሾሙ።

እነዚህንም ይመልከቱ

  • የትግራይ ግጭት
  • 2020 በኢትዮጵያ

ዋቢ

Tags:

የትግራይ ሽግግር መንግሥት ዳራየትግራይ ሽግግር መንግሥት የሽግግር መንግሥት ፍጥረትየትግራይ ሽግግር መንግሥት አመራር እና መዋቅርየትግራይ ሽግግር መንግሥት ስልጣናትየትግራይ ሽግግር መንግሥት የግዛት ቁጥጥርየትግራይ ሽግግር መንግሥት እነዚህንም ይመልከቱየትግራይ ሽግግር መንግሥት ዋቢየትግራይ ሽግግር መንግሥትሕዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይትግራይ ክልል

🔥 Trending searches on Wiki አማርኛ:

ቆጮክፍያካናዳህይወትተምርየሲዳማ ባሕላዊ ሐይማኖትቀልዶችጂጂቴሌቪዥንጥናትዝሆንሰንደቅ ዓላማእንጦጦየልም እዣትዋሽንትአቡነ አረጋዊየኢትዮጵያ ነገሥታትነጋሽዴሞክራሲብረታኝታሪክየምድር መጋጠሚያ ውቅርአፈወርቅ ተክሌሐመልማል አባተቀን በበቅሎ ማታ በቆሎጥምቀትእያሱ ፭ኛዛጔ ሥርወ-መንግሥትሀመርግድግዳደቡብ ሱዳንየማርቆስ ወንጌልየኢትዮጵያ ቋንቋዎችሰለሞንቦሌ ክፍለ ከተማክርስቲያኖ ሮናልዶበግገብረ ክርስቶስ ደስታ ግጥሞችሥልጣኔያማርኛ ሰዋስው (1948)ህሊናመጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤልአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጭየኩሽ መንግሥትውሻሄፐታይቲስ ኤፈረንሣይአርጀንቲናደቡብ አሜሪካአክሱም መንግሥትብረትፍትሐ ነገሥትኒው ዮርክ ከተማቆንጣጭ እርግጥአረቄየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስመጥምቁ ዮሐንስውሃጋኔንትንቢተ ዳንኤልጥር ፮የዮሐንስ ራዕይየአጼ ቴዎድሮስ ዜና መዋዕል - ባልታወቀ ደራሲሀዲያገድሎ ማንሣትክስታኔየኢትዮጵያ ሕዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክሸዋአፍሪቃደቡብ ቻይና ባሕርአፍሮ እስያዊ ቋንቋዎችመንግሥተ አክሱምየአጼ ተክለጊዮርጊስ ዜና መዋዕል🡆 More