ሳንኮሬ ማድራሣ በቲምቡክቱ፣ ማሊ መንግሥት፣ ከ981 እስከ 1585 ዓም ያህል የቆየ የእስልምና መስጊድና ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ወይም ዩኒቨርሲቲ ነበረ። ከቲምቡክቱ ዩኒቨርሲቲ ሦስት ተቋማት መጀመርያው የተመሠረተው ነበር።
መስጊዱ የተመሠረተው በ981 ዓም በቲምቡክቱ ዳኛ በአል-ቃዲ አቂብ ነበረ። ከ1100 ዓም ያህል በፊት በአንዲት ሀብታም ማንዲንካ ወይዘሮ እርዳታ፣ ሕንጻው ሰፊ ማድራሣ (ተቋም) ሆነ። ያንጊዜ የአውሮፓ ትልቅ ዩኒቨርሲቲዎች ገና ምንም ሳይኖሩ፣ ለአፍሪካ ከፍተኛ ደረጃ ተማሮች ግን የእስላም ማድራሦች በቲምቡክቱ፣ በካይሮ እና በሞሮኮ ተገኝተው ነበር።
በ1200 ዓም ግድም የተማሮች ቁጥር 25,000 ነበር፤ የከተማውም ሕዝብ ቁጥር ያንጊዜ 100,000 ነበር። በተለይ ከ1300 ዓም በኋላ በጣም ስመ ጥሩ ትምህርት ተቋም ሆነ።
የተቋሙ መደበኛ ቋንቋ አረብኛ ነበር። በተማሮች መጀመርያ ዓመት ቁራኑን ሙሉ በአረብኛ ከልብ መዳግም ነበረባቸው። ዋና የጥናት ዘርፎች እስልምና፣ ቁራን፣ ሕግና ሥነ ጽሑፍ ነበሩ። በተጨማሪ ሕክምና፣ ቀዶ ጥገና፣ ሥነ ፈለክ፣ ትምህርተ ሂሳብ፣ የተፈጥሮ ሕግጋት ጥናት፣ የጥንተ ንጥር ጥናት፣ ፍልስፍና፣ የቋንቋ ጥናት፣ መልክዓ ምድር፣ ታሪክና ሥነ ጥበብ ጥናቶች አስተማሩ። ከዚያ በላይ ተማሮች ንግድ ወይም ሙያ ይማሩ ነበር፦ አናጢነት፣ ግብርና፣ አሣ ማጥመድ፣ ግንባታ፣ ጫማ መሥራት፣ ልብስ ሰፊነት፣ ወዘተ. ይማሩ ነበር።
በ1319 ዓም ሁለተኛ ማድራሣ ጂንገሬ በር ተቋም ተሠራ፤ በ1392 ዓም ሦስተኛው ተቋም ሲዲ ያህያ ተሠራ ። እነዚህ ሦስት ማድራሦች፣ ሳንኮሬ፣ ጂንገሬ በር እና ሲዲ ያህያ፣ አንድላይ የቲምቡክቱ ዩኒቨርሲቲ ይባሉ ነበር። በ1460 ዓም ቲምቡክቱ ከማሊ መንግሥት ወደ አዲሱ ሶንግኃይ መንግሥት ዓለፈ። በ1585 ዓም ግን የሞሮኮ ወራሪ ሃያላት ማድራሦቹን አጠፉ፣ ብዙ መጻሕፍት ቤቶችንም አቃጠሉ። ቢሆንም ከማድራሣው 70,000 ያህል ሰነዶች እስካሁን ተርፈዋል፣ ዛሬም እየተነተኑ ነው።
ዝነኛ አስተማሮች፦
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article ሳንኮሬ ማድራሣ, which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.