ዚምባብዌ

የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው።

Republic of Zimbabwe
የዚምባᎆ ሬፑብሊክ

የዚምባብዌ ሰንደቅ ዓላማ የዚምባብዌ አርማ
ሰንደቅ ዓላማ አርማ
የዚምባብዌመገኛ
የዚምባብዌመገኛ
ዋና ከተማ ሀራሬ
ብሔራዊ ቋንቋዎች እንግሊዝኛ
መንግሥት
ፕሬዚዳንት
 
ኤመርሰን ምናንጋጓ
የመሬት ስፋት
አጠቃላይ (ካሬ ኪ.ሜ.)
 
390,580 (59ኛ)
ገንዘብ የዚምባብዌ ዶላር
ሰዓት ክልል UTC +2
የስልክ መግቢያ +263

ታሪክ

ከተገዢነት በፊት

የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር።

በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ።

የሮዴዢያ ጊዜ

በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው።

የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል።

ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች።

የሰፋሪዎች አመራርና የእርስ -በርስ ጦርነት

በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ።

የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር።

የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ።

በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ።

ሙጋቤ በ ኅዳር 12 ቀን 2010 ዓም ማዕረጋቸውን ተዉ።


Tags:

ዚምባብዌ ታሪክዚምባብዌሞዛምቢክቦትስዋናአፍሪካዛምቢያደቡብ አፍሪካ

🔥 Trending searches on Wiki አማርኛ:

ዴርቶጋዳግብረ ስጋ ግንኙነትገብረ ክርስቶስ ደስታ ግጥሞችእግር ኳስቅድስት አርሴማኢራቅድመትወላይታየኮንሶ ባህላዊ የእርከን ስራየተፈጥሮ ሕግጋት ጥናትቴዲ አፍሮሕግ ገባመካከለኛ አሜሪካመስተዋድድመካከለኛ ዘመንየስልክ መግቢያጳውሎስ ኞኞወሎኢንዶኔዥያኮንታደጃዝማች ኪዳኔ ወልደመድኅንድፋርሳየኣማርኛ ፊደልረጅም ልቦለድየኦዞን ንጣፍናዚ ጀርመንአክሱም መንግሥትየፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽንቁርአንአቡጊዳአስርቱ ቃላትኢስታንቡልየቋንቋ ጥናትፈተና፤ የዕንባ ጉዞዎች እና ሌሎች ግጥሞችየኢትዮጵያ ቋንቋዎችተረትና ምሳሌሸለምጥማጥመድኃኒትየንቅያ ጸሎተ ሃይማኖት1074 እ.ኤ.አ.ኦሮሞአቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞአውራሪስአክሱምምሳሌናይጄሪያአባይ ወንዝ (ናይል)አሜሪካየኢትዮጵያ ሙዚቃጴንጤቅዱስ ጴጥሮስኩኩ ሰብስቤሥላሴየካ ክፍለ ከተማፍቅር በአማርኛወይራጨዋታዎችአብርሀም ሊንከንፕሉቶቤተ መስቀልጤና ኣዳምሳህለወርቅ ዘውዴዌብሳይትአብርሐምፍቅርሰኞመጥምቁ ዮሐንስየሩዋንዳ የዘር ማጥፋት ወንጀልሥነ ጽሑፍየቅድስት ድንግል ማርያም ስሞች🡆 More