ፖድጎሪጻ (Подгорица) የሞንቴኔግሮ ዋና ከተማ ነው።
በ1995 ዓ.ም. በተደረገ ቆጠራ መሠረት የሕዝቡ ቁጥር 136,473 ነበር።
«ፖድጎሪጻ» ማለት «ከጎሪጻ ሥር» ማለት ነው። «ጎሪጻ» ማለት ደግሞ «ትንሽ ተራራ» ሲሆን ቅርብ የሆነ ኮረብታ ስም ነው።
በጥንትና በሮማ መንግሥት ዘመናት ከሥፍራው አጠገብ «ዶክሌያ» (Doclea) የተባለ መንደር ነበር። የሮማ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ከዚህ አገር ነበር። ስለዚህ ከሱ በኋላ የዚያ ቦታ ስም «ድዮክሌያ» (Diocleia) ሆነ። በስላቮች ይህ ስም «ዱክልያ» (Дукля) ሆነ።
ፖድጎሪጻ መጀመርያ Bizirminium («ቢዚርሚኒዩም») ተባለ። ከ12ኛው ምዕተ ዓመት ጀምሮ «ሪብኒጻ» (Рибница) ተብሎ ከ1318 ዓ.ም. ጀምሮ «ፖድጎሪጻ» በሚለው ስም ታወቋል። ሆኖም ከተማው ከ1937 እስከ 1984 ዓ.ም. ድረስ «ቲቶግራድ» (Титоград) ተሰይሞ ነበር።
ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article ፖድጎሪጻ, which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.