ጎንደር አፄ ቴዎድሮስ ጥያራ ጣቢያ በታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ በስተደቡብ አሥራ ስምንት ኪሎሜትር ርቀት፣ ከባሕር ወለል ፩ሺ ፱መቶ ፺፬ ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኝ አየር ጣቢያ ነው። በየቀኑ በአማካይ ፭ በረራዎች ከጎንደር ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ይደረጋሉ።
ጎንደር ዓፄ ቴዎድሮስ ጥያራ ጣቢያ | |
ከፍታ | 6541 ጫማ (1994 ሜትር) |
ይህ ጥያራ ጣቢያ ለአገር ውስጥ በረራ ብቻ በማገልገል ላይ ሲሆን ማኮብኮቢያው አስፋልት የለበሰ ባለ ፪ሺ ፯መቶ ፹ ሜትር ርዝመት በ ፵፭ ሜትር ስፋት ያለው ነው። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቦይንግ ፯መቶ፴፯ እና ቦምባርዲዬ ጥያሮች በየዕለቱ ከዚህና ወደዚህ ጣቢያ ይበርራል።
ጎንደር ዓፄ ቴዎድሮስ ጥያራ ጣቢያ ታሪካዊቷን የጎንደር ከተማ እና በአካባቢው የሚገኙትን የጎብኚ ተስህቦዎችን፣ እንዲሁም ጣና ሐይቅ፤ የሰሜን ተራራን እና የመሳሰሉትን ለመጎብኘት አማካይ የሆነ ጣቢያ ነው።
ጎንደር አፄ ቴዎድሮስ ጥያራ ጣቢያ በታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ በስተደቡብ አሥራ ስምንት ኪሎሜትር ርቀት፣ ከባሕር ወለል ፩ሺ ፱መቶ ፺፬ ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኝ አየር ጣቢያ ነው። በየቀኑ በአማካይ ፭ በረራዎች ከጎንደር ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ይደረጋሉ።
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article ጎንደር ዓፄ ቴዎድሮስ አየር ማረፊያ, which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.