የትነበርሽ ንጉሴ: የትነበርሽ

የትነበርሽ ንጉሴ በኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ እና የአካል ጉዳተኛ መብትቶች ተሟጋች ናት ፡ እ.ኤ.አ በ 2017 የአካል ጉዳተኞችን መብቶችን እና ማካተቶችን በማስተዋወቅ እንዲሁም  በማኅበረሰቡ ውስጥ ያሉየአእምሮ ውቅርን መለወጥ የሚያበረታታ ሥራዋ  ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድን ተሸልማለች።

የቀደመ ህይወት እና ትምህርት

የትነበርሽ ንጉሴ የአይን ብርሃኗን ያጣችው በ 5 ዓመቷ ነበር ። ይህ አጋጣሚ በተወለድችበት በአማራ ክልል በስፋት ይተገበር ከነበረው ያለ አድሜ ጋብቻ  አንድታመልጥ እድሉን እንደፈጠረላት ትናገራለች። ፡፡የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቷን በሻሸመኔ ካቶሊክ የዓይነ ስውራን  ት/ቤት ተከታትላ ወደ ዳግማዊ  ምኒልክ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (አካታች ትምህርት ቤት) ገብታ እስከ 12 ኛ ክፍል እዚያ ተማረች። በትምህርት ቤቱ ካላት አካዳሚክ ተሳትፎ በተጨማሪ የተማሪዎችን አማካሪ ጨምሮ ከ 6 በላይ የክለቦችን ክበባት መርታለች ፡፡ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን በመቀላቀል የመጀመሪያ ዲግሪ በሕግ ሁለተኛ ዲግሪ በማኅበራዊ ሥራ አግኝ ታለች፡፡ ከመደበኛ ትምህርት ውጭ  በልዩ ልዩ እንቅስቃሴዎች ውስጥ በተከታታይ  ትሳተፋለች በዚህም  የመኢአድ የፀረ ኤድስ እንቅስቃሴን ከ2004 - 05 በመምራት በ 2006 የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ (አአዩ) ሴት ተማሪዎች ማህበርን በመመስረት እንዲሁም የማህበሩ የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት በመሆን  አገልግላለች ፡፡

እንቅስቃሴ

ለሴት ልጆች ትምህርትን አጥብቃ በመስራቷ እ.ኤ.አ. በ 2003 በደቡብ አፍሪካ የተቀበለችውን የአማኒታሪ ሽልማትን (አፍሪካዊ አጋርነት ለወሲባዊ እና ስነተዋልዶ ጤና እና የሴቶች መብቶች ) ጨምሮ ለፀረ-ኤድስ እንቅስቃሴ ባገለገለችበት ወቅት በርካታ ብሔራዊ እና ዓለም አቀፍ ሽልማቶችን አግኝታለች ። ፡፡ ወ / ሮ የትነበርሽ ከአካዳሚክ ህይወቷ ባሻገር በበጎፈቃደኝነት ከ 20 በላይ ድርጅቶች ውስጥ ያገለገለች ሲሆን ከነዚህም ውስጥ በኢትዮጵያ ዓይነ ስውራን የሴቶች ክንፍ ማህበር ለ 4 ዓመታት (እ.ኤ.አ. ከ 2003 እስከ 2007) መርታለች ፡፡ ከዚያም በመቀጠል የአካል ጉዳተኞች ኢኮኖሚያዊ መብትን ጨምሮ በተለያዩ የልማት መርሃ ግብሮች ውስጥ እንዲካተቱ ለማበረታታት የኢትዮጵያ የአካል ጉዳተኞችና የልማት ማዕከል (ኢ.ሲ.ዲ.ዲ.) የተባለ አገር በቀል ድርጅት ለማቋቋም ወሰነች ፡፡ከ2016 ጀምሮ ደግሞ  ቀደም ሲል በዓለምአቀፍ አምባሳደሮች  ቦርድ አባልነት ወክላው  ከነበረው የአካል ጉዳተኞች እና ልማት ብርሃን ለኣለም መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት  ጋር በመተባበር ላይ ትሰራለች ፡

                         የትነበርሽ ንጉሴ" የአካል ጉዳተኞችን መብትና ማካተት በማስተዋወቋ እና ሙሉ አቅማቸውን እንዲገነዘቡ የሚያስችላቸው አነቃቂ ሥራ  በመስራት በማህበረሰቡ ውስጥ የአስተሳሰብ ለውጥ በመፍጠሯ"  እ.ኤ.አ. በመስከረም ወር 2017 ላይ የተባበሩት መንግስታት ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድ ፣ “አማራጭ የኖቤል ሽልማት” ፡ ". ክብሩን ከKhadija Ismayilova, Colin Gonsalves, እና የአሜሪካ የአካባቢ ጠበቃRobert Bilott. ጋር  በመጋራት ተሸላሚ ሆናለች።ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድን በማሸነፏ እና በሄለን ኬለር ሽልማት  መንፈስ  የተበረታታችው የትነበርሽ ንጉሴ በህይወታቸው እና በስራ መስካቸው  ታላቅ ውጤት ያስመዘገቡ የአካል ጉዳተኛ ሴቶችን ለማክበር ከብርሃን  ለኣለም ጋር በመሆን ‹የእርሷ ችሎታዎች ሽልማትን› ኣስጀምራለች ፡፡ www.her-abilities-award.org

ህትመቶች

  • የትነበርሽ ንጉሴ ፣ (2006) በኢትዮጵያ የአካል ጉዳተኞች መብቶች ላይ የሕግ ማሻሻያ አስፈላጊነት ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፣ የሕግ ፋኩልቲ ፣ አዲስ አበባ ኢትዮጵያ ፡፡
  • የትነብርሽ ንጉሴ ፣ እና ፣ ራንሰም ቦብ (2008). የተባበሩት መንግስታት የአካል ጉዳተኞች መብቶች ኮንቬንሽን የድህነት ፣ በረሃብ ፥ ኣቅርቦት አጥረት አንዲሁም መገለል ዙሪያ ላይ የአንቅስቃሴ ጥሪ ፣ ኢ.ሲ.ዲ.ዲ. ፣ አዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ
  • የትነበርሽ ንጉሴ ፣  (2009) የአካል ጉዳተኞች የሥነ-ልቦና ልኬቶች እና የሥራ ስምሪት ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፣ የማኅበራዊ ሥራ ትምህርት ቤት ፣ አዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ ፡፡

ሽልማቶች

  • የጾታ እና የስነ ተዋልዶ ጤና ተሟጋቾች የ AMANITARE ሽልማት ፣ እ.ኤ.አ. 2003 ፣ ጆሃንስበርግ ፣ ደቡብ አፍሪካ ፡
  • የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከአዲስ አበባ ኤች.አይ.ቪ / ኤድስ መከላከያና ቁጥጥር ጽህፈት ቤት (ኤች.ፒ.ኮ.) ጋር በመተባበር እጅግ በጣም ጥሩ የኤች.አይ.ቪ / ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር እንቅስቃሴ ማስተባበር የግለሰብ ሽልማት ፡፡ ጥቅምት 7 ቀን 2005 አዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ ፡፡
  • በጄኔራል ሜዲካል ሐኪሞች ማህበር የተሰጠው ምርጥ የኤች.አይ.ቪ / ኤድስ ብሔራዊ አክቲቪስት ፣ 2005 ፣ አዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ ፡፡
  • የዓለም የልዩነት 100 ሽልማት ፣ በዓለም አቀፍ የሴቶች (ቲአአዋ) ተሸልሟል ፡
  • ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድ
  • የሄለን ኬለር መንፈስ 2018 [1] Archived ጁን 22, 2019 at the Wayback Machine

ማጣቀሻዎች

Tags:

የትነበርሽ ንጉሴ የቀደመ ህይወት እና ትምህርትየትነበርሽ ንጉሴ እንቅስቃሴየትነበርሽ ንጉሴ ህትመቶችየትነበርሽ ንጉሴ ሽልማቶችየትነበርሽ ንጉሴ ማጣቀሻዎችየትነበርሽ ንጉሴራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድኢትዮጵያ

🔥 Trending searches on Wiki አማርኛ:

መናፍቅየኢትዮጵያ ሶማሊያ ጦርነትሰጎንሙላቱ አስታጥቄቡርኪና ፋሶየኢንዱስትሪ አብዮትከነዓን (ጥንታዊ አገር)አዲስ አበባማጎግአምልኮኣበራ ሞላእንስሳክርስትናዓለማየሁ ገላጋይአባይሜክሲኮፕሮቴስታንትቅድስት አርሴማራስ መኮንንየደም መፍሰስ አለማቆምወንጌልኤምባሲመስቀልዋናው ገጽ/ለጀማሪወች/ፊደል አጻጻፍጨዋታዎችግራኝ አህመድዓሣሻታውኳንፋስ ስልክ ላፍቶፋርስኛባክቴሪያመሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲፍቅር በአማርኛቁስ አካላዊነትሙዚቃጠላየጢያ ትክል ድንጋይብር (ብረታብረት)ወምበር ገፍየኢትዮጵያ ሕግከተማአሊ ቢራቁርአንሥነ-ፍጥረትሰባአዊ መብቶችሀዲያድፋርሳሲንጋፖርባሻጣልያንትምህርተ፡ጤናሐረግ መምዘዝተውሳከ ግሥቁስ አካልአፄንብየኢትዮጵያ ነገሥታትየኢትዮጵያ ቋንቋዎችሥነ ምግባርማርችየመጀመሪያው የዓለም ጦርነትቤተ ጎለጎታኣደስመካከለኛ ዘመንየሐበሻ ተረት 1899የአዋሽ በሔራዊ ፓርክጀርመንኛዓለም-አቀፍ መደበኛ የመጽሐፍ ቁጥርየኢትዮጵያ ሙዚቃ640 እ.ኤ.አ.ኮምፒዩተርንጉሥየንቅያ ጸሎተ ሃይማኖት🡆 More