ትግራይ ከ ኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ ትዋሰናለች። ዋና ከተማዋ መቐለ ነው። ሌሎች ታዋቂ ከተሞች ውቅሮ፣ ዛላምበሳ፣ ዓብዪዓዲ ፣ዓድዋ፣ ነበለት፣ ሸራሮ፣ዓዲግራት፣ አኽሱም፣ ሽረ እንዳስላሰ፣ ማይጨው፣ ናቸው። የሕዝብ ብዛት በ1999 ህዝብ እና ቤት ቆጠራ መሰረት 7.9 ሚልዮን ነው። ትግርኛ የክልሉ ዋና ቋንቋ ነው። እምባ ኣላጀ፣ ፅበት እና ወርሐት በትግራይ ሀገር ያሉ ከፍተኛ ቦታዎች ናቸው። ትግራይ በርካታ ተፈጥሯዊ፣ ባህላዊና ታሪካዊ ሃብቶች የታደለ ሀገር ነው። የ2000 ዓመት የሓ ጥንታዊ ቤተ መቅደስ፣ የ1500 ዓመት የአክሱም ጥንታዊ ሃውልቶች፣ከ4ኛው እስከ 18ኛው ክ/ዘመን እንደተሰሩ የሚታወቀው ከ120 በላይ የሚሆኑ ከኣለት ድንጋይ ተፈልፍለው የተሰሩ ውቅር ኣብያተክርስትያናትና ገዳማት እንዲሁም ሌሌች በርካታ ታሪካዊና ኣርኪኦሎጂካዊ ስፍራዎች የሚገኙበት ሀገር ነው። ትግራይን በባህልና በታሪካዊ ኣመጣጥ ከኤርትራ ነጥሎ ማየት ኣይቻለም። ከኣምሓራ ቀጥሎ የዳኣማትና የአክሱም ግእዛዊ ሥልጣኔ ባለቤት ናት። ዓድዋ
ትግራይ | |
ክልል | |
የትግራይ ሀገርን በቀይ የሚያሳይ የኢትዮጵያ ካርታ | |
አገር | ትግራይ |
ርዕሰ ከተማ | መቐለ |
የቦታ ስፋት | |
• አጠቃላይ | 50,286 |
የሕዝብ ብዛት | |
• አጠቃላይ | 9,201,000 |
This article uses material from the Wikipedia አማርኛ article ትግራይ ክልል, which is released under the Creative Commons Attribution-ShareAlike 3.0 license ("CC BY-SA 3.0"); additional terms may apply (view authors). Content is available under CC BY-SA 4.0 unless otherwise noted. Images, videos and audio are available under their respective licenses.
®Wikipedia is a registered trademark of the Wiki Foundation, Inc. Wiki አማርኛ (DUHOCTRUNGQUOC.VN) is an independent company and has no affiliation with Wiki Foundation.